ኮሮናቫይረስ፡ ጣልያን ውስጥ በአንድ ቀን ብቻ 133 ሰዎች ሞተዋል

ኮሮናቫይረስ

Image copyrightGETTY IMAGES
በየዘመኑ ወረርሽኞች የሚሊዮኖችን ሕይወት ቀጥፈዋል። ሕክምና በዘመነበት ዘመን በመፈጠራችን በሽታዎች እንደተፈለፈሉ በአጭሩ ስለሚቀጩ የቀድሞ ትውልድ ወረርሽኝ እንደሚያስጨንቀው እኛን ላያስጨንቀን ይችላል።
ኮሮናቫይረስ ግን አሁን ዓለምን ሰቅዞ ይዟል። አገራት ምጣኔ ሐብታቸው ብርክ ይዞታል። የዓለም 'የምርት ፋብሪካ' የምትባለው ቻይና እንኳን ኮሮና ፍዳዋን እያበላት ነው።
በቁጥር ከዩናይትድ ኪንግደምን ሕዝብ የሚልቀውን የሁቤ ግዛት ነዋሪ ከቤትህ ንቅንቅ እንዳትል ብላዋለች። 60 ሚሊዯን የሚጠጋው የግዛቲቱ ነዋሪ አምራች ሕዝብ ቤቱ ሲቀመጥ ቻይና በድምሩ የምታጣው ገንዘብ የዋዛ አይሆንም።
በሰሜን ጣሊያን ሎምባርዲ ክልል 16 ሚሊዮን ሰዎች ገለል ተደርገው እንዲቀመጡ አድርጋለች። ይህ ቁጥር የሕዝቧ አንድ አራተኛ ይጠጋል። በነዚህ የእንቅስቃሴ እቀባ በተደረገባቸው 14 አውራጃዎች አይደለም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ሰርግና ቀብር እንኳ በሰዎች ስብስብ መሀል እንዳይከወን ተወስኗል። ይህ ደንብ የቱሪስት መዳረሻ የሆኑትን ሚላንና ቬነስን ይመለከታል። የጣልያን ሴሪ-አ ጨዋታዎችም በባዲስ ስታድዬም ተከናውነዋል።
በቻይና ጉዋንዡ ከቫይረሱ የሚያገግሙ ሰዎች የሚጠለሉበት ባለ አምስት ፎቅ ሆቴል ተደርምሶ 10 ሰዎች ሞተዋል፤ 28ቱ ፍለጋ ላይ ናቸው። 70ዎቹ ፍርስራሽ ተጭኗቸዋል። የሕንጻው ባለቤት በፖሊስ ቁጥጥር ውሏል።

Post a Comment

0 Comments