በቅርቡ በቻይና ሁቤይ ግዛት ውሃን ከተማ የተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት በመዛመት ላይ ይገኛል።
አሁን ላይም ቫይረሱ ከ70 በላይ በሆኑ የዓለም ሀገራት ውስጥ መስፋፋቱን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
በዚህ መሰረትም በአፍሪካ ከናይጄሪያ፣ ግብጽ እና አልጄሪያ በተጨማሪ ሞሮኮ፣ ቱኒዚያ እና ሴኔጋል ቫይረሱ የተገኘባቸው ሌሎች ሀገራት መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡
በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በቫይረሱ ከ 3ሺህ 100 በላይ ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ፥ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ90 ሺህ በላይ ሆኗል።
ጭ፥ ቢቢሲ እና ሲ ቢ ኤስ

0 Comments