ቱኒዚያ በኮሮናቫይረስ የመጀመሪያውን የሞተ ሰው ይፋ ስታደርግ፤ ኒጀር በበኩሏ በአገሪቱ የመጀመሪያውን በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን አስታውቃለች።
በቱኒዚያ በኮሮናቫይረስ ህይወታቸው ያለፈው ከአራት ቀናት በፊት ከቱርክ ወደ ቱኒዚያ የተጓዙ የ72 ዓመት ሴት ናቸው ተብሏል።
ኒጀር በበኩሏ ከቶጎ የመጣ የ36 ዓመት ጎልማሳ በኮሮናቫይረስ መያዙን አረጋግጫለሁ ብላለች።
ይህ ግለሰብ ወደ ኒጀር ከመግባቱ በፊት ባለፉት ጥቂት ቀናት ወደ ቶጎ፣ ጋና፣ አይቮሪኮስትና ቡርኪናፋሶ ተጉዞ ነበር ተብሏል።
ቱኒዚያ የመጀመሪያ በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው መኖሩን ይፋ ያደረገችው ከ18 ቀናት በፊት ሲሆን ዛሬ ላይ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቁጥር 39 ደርሷል።
እስካሁን አፍሪካ ውስጥ 7 ሰዎች በግብጽ፣ 9 በአልጄሪያ፣ 2 በሞሮኮ እንዲሁም ሱዳን እና ቡርኪናፋሶ እያንዳንዳቸው አንድ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎችን አስመዝግበዋል።

0 Comments