
• ኢራን ውስጥ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። በ 24 ሰዓታት ውስጥ የሟቾች ቁጥር ከ 724 ወደ 853 ከፍ ብሏል ፡፡
• ኢትዮጵያ የኮሮና ተህዋሲ ስርጭትን ለመግታት ለ 15 ቀናት ትምህርት ቤቶችን መዝጋቷን ተከትሎ ተማሪዎች ወደየቤታቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
• በኢትዮጵያ በሶስት ቀናት ውስጥ በኮሮና ተሕዋሲ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አምስት ደረሰ። አምስተኛው ሰው በተሕዋሲው መያዛቸው በትናንትናው ዕለት መረጋገጡን የጤና ምኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በትዊተር ገፃቸው አስፍረዋል።
• ኢትዮጵያ ለሚቀጥሉት አስራ አምስት ቀናት ትምህርት ቤቶች፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችና ትላልቅ ስብሰባዎችን ከለከለች። የአገሪቱ 45 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ባሉበት ትምህርታቸውን ይቀጥላሉ ተብሏል።
• ጀርመን ከዛሬ ጠዋት አንስቶ የኮሮና ተህዋሲ ስርጭትን በመስጋት የሚያዋስንዋትን የአምስት ሃገር ድንበሮች ዘጋች።
0 Comments