AFP
የአውሮፓ ህብረት ከአባላት አገራቱ ዜጎች ውጪ የሚመጡ ሰዎችን ለ30 ቀናት እንዳይገቡ ሊከለክል መሆኑ ተሰማ።
ውሳኔው በ26ቱ የአውሮፓ አገራት እንዲሁም አይስላንድ፣ ኖርዌይ፣ ስዊዘርላንድና ሌቺቴንስቴይን ያካትታል ተብሏል።
ይህ ውሳኔ የዩናይትድ ኪንግደም ዜጎች አይመለከታቸውም።
በአውሮፓ ቫይረሱ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን 8ሺህ ያህል ሰዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ መሞታቸው ተመዝግቧል።
በተያያዘ ዜና ዩሮ 2020 የእግር ኳስ ጨዋታ በአንድ ዓመት መገፋቱ ይታወሳል።
እንደ ዓለም አቀፉ ጤና ድርጅት መረጃ እስካሁን ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ 200ሺህ ሰዎች ያህል በቫይረሱ ተይዘዋል።

0 Comments