በኬኒያ በኮሮና የተያዙ ሰዎች ቁጥር ሰባት ደረሰ

ኬኒያ ቫይረሱ ከተገኘባቸው አገራት የሚመጡ የውጪ ዜጎች ወደ አገሯ እንዳይገቡ ከልክላለች


ኬኒያ በዛሬው ዕለት ሦስት በቫይረሱ የተያሱ ሰዎችን ማግነቷን ገለፀች።
ይህ በአጠቃላይ በአገሪቷ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርን ሰባት አድርሶታል።
የጤና ሚኒስትር የሆኑት ሙታኢ ካግዌ እንዳሉት ሁሉም ሕሙማን ከባህር ማዶ ወደ ኬኒያ የመጡ ናቸው ብለዋል።
አሁን የተገኙት ሰዎች ከስፔን በዱባይ በኩል የመጡ ጥንዶች እንደሆኑ ተነግሯል።
ሌላኛው ሕሙም ብሩንዲያዊ ሲሆኑ ከዱባይ መምጣታቸው ተነግሯል። መንግሥት ከእነዚህ ሶስት ሰዎች ጋር የተገናኙትን በሙሉ ክትትል እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ኬኒያ ቫይረሱ ከተገኘባቸው አገራት የሚመጡ የውጪ ዜጎች ወደ አገሯ እንዳይገቡ ከልክላለች።

Post a Comment

0 Comments