Getty Images
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ምግብ ቤቶች ደንበኞቻቸው ወደ ምግብ ቤቱ ከመግባታቸው በፊት እጃቸውን በሳኒታይዘር እንዲያጸዱ እያደረጉ ነው።
ደቡብ አፍሪካ በአንድ ቀን ብቻ 23 በኮሮና የተያዙ ሰዎችን በማግኘት ከፍተኛውን ቁጥር አስመዘገበች።
ከ23ቱ ሰዎች መካከል 4ቱ እድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል።
አሁን በደቡብ አፍሪካ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ 85 ሰዎች ይገኛሉ።
የአገሪቱ ጤና ጥበቃ ሚንስትር 8ቱ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙት እዛው ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከሌሎች ሕሙማን ጋር በነበራቸው ንክኪ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፖሳ ኮሮና በብዛት ከሚገኝባቸው አገራት ወደ ደቡብ አፍሪካ ይደረጉ የነበሩ በረራዎችን መሰረዛቸው እና ብሔራዊ አደጋ ማወጃቸው ይታወሳል።

0 Comments