በኢትዮጵያ ኮረናቫይረስ ያለበት ስድስተኛ ሰው ተገኘ የጤና ጥበቃ ሚንስትሯ ሊያ ታደሰ ቫይረሱ የተገኘባት የ59 ዓመት ኢንግሊዛዊት ሴት ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ የመጣች መሆኗን አሳውቀዋል።
እንግሊዛቷ ዲፕሎማት በነበረችበት ሆቴል እራሷን አግልላ መቆየቷን የጤና ሚንስትሯ አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከግለሰቧ ጋር ንክኪ የነበራቸውን ሰዎች የመለየትና የክትትል ስራ አጠናክሮ መቀጠሉም ተነግሯል።
በአሁኑ ሰዓት ግለሰቧ በለይቶ የህክምና መስጫ ማዕከል የቅርብ የሕክምና ክትትል እየተደረገላት እንደሆነ የተጠቆመ ሲሆን፤ ህብረተሰቡም በሁኔታዎች ሳይደናገጥ በተረጋጋ መንፈስ የበሽታውን ስርጭት በመግታት የሚቻለውን ሁሉ እንዲያደርግ ተጠይቋል።

0 Comments