በኢትዮጵያ ኮረናቫይረስ ያለበት ስድስተኛ ሰው ተገኘ




Health check at Ethiopian airports

በኢትዮጵያ ኮረናቫይረስ ያለበት ስድስተኛ ሰው ተገኘ የጤና ጥበቃ ሚንስትሯ ሊያ ታደሰ ቫይረሱ የተገኘባት የ59 ዓመት ኢንግሊዛዊት ሴት ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ የመጣች መሆኗን አሳውቀዋል።
እንግሊዛቷ ዲፕሎማት በነበረችበት ሆቴል እራሷን አግልላ መቆየቷን የጤና ሚንስትሯ አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከግለሰቧ ጋር ንክኪ የነበራቸውን ሰዎች የመለየትና የክትትል ስራ አጠናክሮ መቀጠሉም ተነግሯል።
በአሁኑ ሰዓት ግለሰቧ በለይቶ የህክምና መስጫ ማዕከል የቅርብ የሕክምና ክትትል እየተደረገላት እንደሆነ የተጠቆመ ሲሆን፤ ህብረተሰቡም በሁኔታዎች ሳይደናገጥ በተረጋጋ መንፈስ የበሽታውን ስርጭት በመግታት የሚቻለውን ሁሉ እንዲያደርግ ተጠይቋል።

Post a Comment

0 Comments