የዓለማችን ቍ. ፩ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች ሰርቢያ ኦርቶዶክሱ ኖቫክስ ጆኮቪች የክትባት ዓለሙን አርበደበደው



✍ ዘርአዳዊት ዘ-ኢትዮጵያ 

ግራንድ ስላም 23፡ የዓለማችን ቍ. ፩ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች ሰርቢያ ኦርቶዶክሱ ኖቫክስ ጆኮቪች የክትባት ዓለሙን አርበደበደው። በትናንትናው ዕለት የፈረንሳይን ክፍት የሸክላ ሜዳ ቴኒስ ውድድር በማሸነፍ ሃያ ሦስተ ግራንድ ስላም ውድድሮችን ያሸነፈ ብቸኛ የቴኒስ ስፖርት ኮከብ ለመሆን በቅቷል።

አውስራሊያ – ፈረንሳይ – ዊምብልደን /እንግሊዝ – አሜሪካ አራቱ የግራንድ ስላም ውድድሮች ናቸው።

ኖቫክ ጆኮቪች ጦርነትን፣ ፌደረርን፣ ናዳልን፣ አልካራዝን፣ አውስትራሊያን አልካታራዝን፣ አሜሪካን፣ ኔቶን፣ አድሏዊ ሚዲያን፣ ጠላትነትን የተሞላበት ህዝብ፣ ወረርሽኝ፣ ግራንድ ስላም ስረዛዎችን፣ ፍትሃዊ ያልሆኑ መመዘኛዎችን እና የግዳጅ ክትባቶችን አሸንፏል። እና አሁን፣ በታሪክ ውስጥ ከየትኛውም ሰው የበለጠ የግራንድ ስላም/ Grand Slam ውድድሮችን አሸንፏል። በስፖርት ታሪክ ውስጥ ትልቁ ታሪክ።

Post a Comment

0 Comments